Friday, November 27, 2015

የአጣጣሚ ሚካኤል የጥገና ፕሮፖዛል


ጥቅምት 2008 ዓ.ም

ክፍል አንድ

የቤተክርስቲያኑ አሰራርና ነባራዊ ሁኔታ


የደብረ ገነት አጣጣሚ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ንጉስ አድባር ሰገድ ዳዊት ተሰርቶ ተጠናቀቀ።  ንጉሰ ነገሥቱ በዘመኑ ከግብጽ አሌክሳንደርያ በመጡት የኢትዮጵያ ጳጳስ አቡነ ክርስቶደሉ ባላባቱና ም ዕመናኑ በተገኙበት ሰኔ 1 ቀን 1709 ተመረቀ።

በአራት ማዕዘን ቅርጽ የተሰራው ይህ ቤተክርስቲያን ግድግዳው በጥቁር ድንጋይና ተቃትሎ ከስድስት ወር እስከ ሁለት ዓመት በውሃ ተዘፍዝፎ በተብላላ ኖራ ተገብቷል።  በሮቹ ከቁስቋም ተጠርቦ በመጣ ቀይ ልዝብ ድንጋይ በቅስት ተጌጡ።  ጣራው በባኅላዊ

Thursday, November 26, 2015

ኑ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ እንስራ!!!!! ነህ 2:20


 ለነፍሳችን ቤዛ የሚሆንልንን መንፈሳዊ ስራ በመስራት የአቅማችንን በማድረግ የተጀመረውን ህንጻ ቤተክርስቲያን ከፍጻሜ እናድርስው፡፡ 

በመጀመርያ ይህን ሁሉ ላደረገ ልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው እንላለን!!

                                                              ለበረከት ተጠርታችኃል


አሁንም፥ እነሆ፥ እግዚአብሔር ለመቅደስ የሚሆን ቤትን ትሠራ ዘንድ መርጦሃልና ጠንክረህ ፈጽመው። (መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 28፡10)


ለዚህም የተቀደሰ አላማ እጃችሁን በመዘርጋት እንድትረዱና የበረከቱ ተካፋይች ትሆኑ ዘንድ ቅዱስ ሚካኤል   ስም እንጠይቃለን፡

ደብረ ገነት አጣጣሚ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ጎንደር እድሳት


Thursday, November 19, 2015

የደብረ ገነት አጣጣሚ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን የዕድሳት ፕላን


ትንቢተ ሐጌ 1፥8
ወደ ተራራው ውጡ፥ እንጨትንም አምጡ፥ ቤቱንም ሥሩ እኔም በእርሱ ደስ ይለኛል፥ እኔም እመሰገናለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር፦