ጥቅምት 2008 ዓ.ም
ክፍል አንድ
የቤተክርስቲያኑ አሰራርና ነባራዊ ሁኔታ
የደብረ ገነት አጣጣሚ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ንጉስ አድባር ሰገድ ዳዊት ተሰርቶ ተጠናቀቀ። ንጉሰ ነገሥቱ በዘመኑ ከግብጽ አሌክሳንደርያ በመጡት የኢትዮጵያ ጳጳስ አቡነ ክርስቶደሉ ባላባቱና ም ዕመናኑ በተገኙበት ሰኔ 1 ቀን 1709 ተመረቀ።
በአራት ማዕዘን ቅርጽ የተሰራው ይህ ቤተክርስቲያን ግድግዳው በጥቁር ድንጋይና ተቃትሎ ከስድስት ወር እስከ ሁለት ዓመት በውሃ ተዘፍዝፎ በተብላላ ኖራ ተገብቷል። በሮቹ ከቁስቋም ተጠርቦ በመጣ ቀይ ልዝብ ድንጋይ በቅስት ተጌጡ። ጣራው በባኅላዊ